=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=
ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ
1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።
2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።
3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።
4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
![]() =<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=
![]() በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። ![]() |
---|
ለከፊሉ እስር ቤት ለቀሪውም ገነት፤
ከፈጣሪዋ ዘንድ እንስ ያለች መሬት፤
ዱንያ ዋጋ ቢሷ ከህልም ያላለፈች፤
በእቅድ በምኞት በባዶ የተሞላች፤
እኛንም ጠራርጋ ገደል ይዛን ገባች፤
አይይቀሬውን ጉዳይ ሞትን አስረስታ፤
በብልጭልጭ ነገር ዳንኪራ አስመትታ፤
ከዚያ ከሠፊ አገር ላታስቀር ጎትታ፤
ከሞት ከሚያስፈራው ከቀብር ጨለማ፤
የዘመድን ጥሪ ከማያሠማ፤
ጌታህ ማነው ከሚል ከከባባድ ጥያቄ፤
ቀረኝ ከማያስብል ወይ ጨርቄን ማቄ፤
ከመቃብር ጭንቀት ከጠለቀው ጉድጏድ፤
አናት ከሚበሳው ከፀሃዩ ንዳድ፤
በየወንጀሉ ልክ ላብን ከሚጠምቀው፤
የጎን አጥንት ከሚያስተላልፈው፤
እናትና ልጅን ከሚያፈራርደው፤
በአፍጢም እየደፋ እሳት ከሚጥለው፤
በባለሠው እሳት ድንጋይ ባነደደው፤
እያገላበጠ ስጋን ከሚጠብሰው፤
ከዘወትር መኖሪያ ማረፊያ ከሌለው፤
መፅሐፍ ቢታተም ፅሁፍ ከማይገልፀው፤
ከዚያ ከሠፊ ሐገር ማንም ከማይቀረው፤
ዱንያ አዘናግታ አስረግጣን ጮቤ፤
ዛሬ ላይ ደረስን ስንል ምንድነው ሃሳቤ፤
የአደም ልጆች ሆይ አናንቀላፋ፤
ነቃ እንበልና ለአኼራ እንልፋ፤
የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ |
---|